ዘላቂነት ያለው ግብርና ከምንጊዜውም በላይ አሁን እጅግ አስፈላጊ ሆኗል። ዘላቂነት ያለው ግብርና የእርሻ መስፈርቶች፣ ገበሬዎች የተሻሉ ሰብሎችን እንዲያመርቱ፣ ምርታማነታቸውን እንዲያሳድጉ፣ ስለ ዘላቂነት አፈጻጸማቸው ጠቃሚ ግንዛቤዎችን እንዲያገኙ እና ኢንቨስትመንቶቻቸውን በትልልቅ ስጋቶቻቸው ላይ እንዲያተኩሩ የሚረዳ ተግባራዊ ማዕቀፍ እና የተመረጡ ፈጠራዎችን ያቀርባል። የእርሻ መስፈርቶቹ የሰርቲፊኬት ባለቤቶች ግብርና በማህበራዊ፣ አካባቢያዊ እና ኢኮኖሚያዊ መስኮች ላይ ያለውን አዎንታዊ ተፅእኖ ከፍ እንዲያደርጉ ለማገዝ የተነደፉ ሲሆን፣ ገበሬዎች መተዳደሪያቸውን እንዲያሻሽሉ እና የሚኖሩበትን እንዲሁም የሚሠሩበትን አካባቢ እንዲጠብቁ አቅም ይፈጥራሉ።
የተሻሻለው ዘላቂነት ያለው ግብርና ስታንዳርድ የእርሻ መስፈርቶች፣ በቀድሞዎቹ እትሞች ላይ የነበሩትን እጅግ ጠቃሚ የሆኑ ነጥቦችን የያዘ ሲሆን በእርሻ ደረጃ ለውጥ የሚያመጡ መሣሪያዎችንም እንደያዘ ይቀጥላል። አላስፈላጊ ሸክም የሚሆኑ መስፈርቶችን ያስወገድን ሲሆን፣ የውስጥ ኢንስፔክሽኖች እና የውሂብ አሰባሰብ ሂደቶችን ይበልጥ አስፈላጊ በሆኑ ጉዳዮች ላይ ብቻ እንዲያተኩሩ አድርገናል። ለገበሬዎች፣ ይህ ማለት አነስተኛ ውስብስብነት እና ለሥራው ትግበራ የሚያስፈልጉ ግብዓቶችን መቀነስ ማለት ነው። ለኩባንያዎች፣ ይህ ማለት ከአካባቢያዊ፣ ማህበራዊ እና አስተዳደራዊ (ESG) ማዕቀፎች እንዲሁም ከዓለም አቀፍ ደንቦች ጋር ይበልጥ የተጣጣመና ከፍተኛ ተፅእኖ ያለው ስታንዳርድ ማለት ነው።