
ርዕስ፦ | የአካባቢ አባሪ |
ኮድ፦ | A-09-SCRL-B-FA |
እትም፦ | 1.3 |
የሚመለከተው፦ | የእርሻ ሰርቲፊኬት ባለቤቶች |
አፈጻጸም፦ | አስገዳጅ ይዘት |
ተፈጻሚነት የሚጀምርበት ቀን፦ | ገና የሚወሰን (TBD) |
የሚያበቃበት ጊዜ፦ | እስከሚቀጥለው ማሳሰቢያ ድረስ |
የታተመበት ቀን፦ | ጳጉሜ 3፣ 2017 ዓ.ም. |
ከሚከተለው ጋር ይገናኛል፦ | |
የሚከተለውን ይተካል፦ |
ይህ ሰነድ ስለ ምንድን ነው?
ይህ አባሪ በሬንፎረስት አሊያንስ ስታንዳርዶች ውስጥ በሚገኘው የአካባቢ ምዕራፍ ስር ለተካተቱት የእርሻ መስፈርቶች ተጨማሪ አስገዳጅ ይዘቶችን ያካትታል።
ይህ ሰነድ የሚከተሉትን ያካትታል፦
የተፈጥሮ ደን ጥበቃ፣ ሌሎች ተፈጥሯዊ ሥነ-ምህዳሮች እና ጥበቃ የሚደረግላቸው አካባቢዎች መሰረታዊ መስፈርቶች ጋር የተያያዙ ተጨማሪ መረጃዎች።
ለዘላቂ ግብርና ስታንዳርድ ከእርሻ ድንበሮች ውጭ ስላሉ የጥበቃ እና የዕድሳት ስራዎች ተጨማሪ ዝርዝሮች።
ለተሃድሶ ግብርና ስታንዳርድ የተፈጥሮ ሥነ-ምህዳሮችን እና እፅዋትን ስለመጠበቅና እና ማልማት የሚገልጹ ተጨማሪ ዝርዝሮች።
ይህንን ሰነድ መቼ እና እንዴት መጠቀም ይቻላል?
ይህ ሰነድ ለሰርቲፊኬት ባለቤቶች (CH) እና ለሰርቲፊኬሽን አካሎች (CB) የተካተቱ መስፈርቶችን እና አፈጻጸማቸውን በተመለከተ ተጨማሪ ዝርዝሮችን ይሰጣል። ሰነዱ በሦስት ክፍሎች የተከፈለ ነው፦
የእርሻ ስታንዳርዶች መሠረታዊ መስፈርቶች
ከዘላቂነት ያለው ግብርና ስታንዳርድ የተወሰዱ መስፈርቶች
በተሃድሶ ግብርና መመሪያ ውስጥ የተቀመጡ መስፈርቶች
መሠረታዊ መስፈርቶች ለሁሉም የእርሻ ስታንዳርዶች ተፈጻሚ ይሆናሉ። በዘላቂነት ያለው ግብርና ስታንዳርድ እና በተሃድሶ ግብርና ስታንዳርድ ክፍሎች ውስጥ የሚገኙ መስፈርቶች፣ ለስታንዳርዶቹ ተግባራዊ የሚሆኑ ልዩ እና/ወይም ቀጣይነት ያለው ማሻሻያ መስፈርቶችን ያካትታሉ።
ከእትም 1.2 ወደ እትም 1.3 የተደረጉ ለውጦች
ክፍል | የተደረገው ለውጥ |
|---|---|
በመላው ሰነዱ | ለጋራ መሠረታዊ መስፈርቶች፣ እንዲሁም ለዘላቂነት ያለው ግብርና ስታንዳርድ እና ለተሃድሶ ግብርና ስታንዳርድ ልዩ መስፈርቶች አጠቃላይ ክፍሎች ተካተዋል። |
መሠረታዊ መስፈርቶች | ለግልጽነት ሲባል የተፈጥሮ ደን ጥበቃ፣ ሌሎች ተፈጥሯዊ ስነ-ምህዳሮች እና ጥበቃ የሚደረግላቸው አካባቢዎች መስፈርቶችን እንደገና ማደራጀት። |
1.5 ለመሠረተ ልማት የታቀደ አነስተኛ የለውጥ ሂደት | ይህ ከEUDR ጋር ለመጣጣም ለሚፈልጉ የኮኮዋ እና የቡና የሰርቲፊኬት ባለቤቶች (CH) የማይፈቀድ መሆኑን ማብራራት። |
ከዘላቂነት ያለው ግብርና ስታንዳርድ የተወሰዱ መስፈርቶች | የቀጣይነት ያለው ማሻሻያ መስፈርቶች 6.2.3 እና 6.2.4 ወደዚህ ክፍል ተዛውረዋል። |
ተሃድሶ ግብርና ስታንዳርድ | ስለ አዲሱ የተሃድሶ ግብርና ስታንዳርድ ልዩ መስፈርቶች ተጨማሪ መረጃዎችን ማካተት። |
የእርሻ ስታንዳርዶች መሰረታዊ መስፈርቶች
ይህ ክፍል ለሬንፎረስት አሊያንስ ዘላቂነት ያለው ግብርና ስታንዳርድ (SAS) እና ለተሃድሶ ግብርና ስታንዳርድ (RAS) መሠረታዊ መስፈርቶች አተገባበር ተጨማሪ ዝርዝሮችን ይሰጣል።
1. የተፈጥሮ ደኖች ጥበቃ፣ ሌሎች ተፈጥሯዊ ሥነ-ምህዳሮች እና ጥበቃ የሚደረግላቸው አካባቢዎች
ይህ ክፍል ከዘላቂ ግብርና ስታንዳርድ የተወሰዱትን የመስፈርት 6.1.1 ለውጥ እና የመስፈርት 6.1.2 ጥበቃ ወደሚደረግላቸው አካባቢዎች ስለመግባት ተጨማሪ መረጃዎችን ይሰጣል።
1.1 ከመስፈርቶች 6.1.1 እና 6.1.2 ጋር የተያያዘ የጂኦዳታ ስጋት ግምገማ
የሬንፎረስት አሊያንስ የጂኦዳታ ስጋት ግምገማ ለሰርቲፊኬት ባለቤቶች (CH) የሚከተሉትን መረጃዎች ያቀርባል፦
የደን ጭፍጨፋ ስጋት ካርታ።
ጥበቃ ወደሚደረግላቸው አካባቢዎች የመግባት ስጋት ካርታ።
እያንዳንዱ የእርሻ ክፍል ያለበትን የደን ጭፍጨፋ እና ጥበቃ ወደሚደረግላቸው አካባቢዎች የመግባት ደረጃ የሚያሳይ የጂኦዳታ ስጋት ሰንጠረዥ።
እነዚህ ውጤቶች ከሬንፎረስት አሊያንስ ስታንዳርድ መስፈርቶች 6.1.1 እና 6.1.2 ጋር ሊኖሩ የሚችሉ አለመጣጣሞችን አጠቃላይ እይታ ይሰጣሉ። የስጋት ግምገማው በሬንፎረስት አሊያንስ የሰርቲፊኬሽን ፕላትፎርም ላይ ለሰርቲፊኬት ባለቤቶች እና ለሰርቲፊኬሽን አካላት የሚገኝ ሲሆን፣ የጂኦሎኬሽን ውሂብ በተሻሻለ ቁጥር መረጃው ወቅታዊ ይሆናል።
1.2 ከመስፈርት 6.1.1 ጋር የተያያዘ የተፈጥሮ ደን እና የተፈጥሮ ስነ-ምህዳሮች አለመለወጥ
መሠረታዊ መስፈርት 6.1.1 ታኅሣሥ 23፣ 2006 ዓ.ም. እንደ የመጨረሻ የጊዜ ገደብ አድርጎ ያስቀምጣል። ከዚህ ቀን በኋላ ምንም ዓይነት የደን ጭፍጨፋ ወይም የለውጥ ሂደት መከናወን የለበትም። ከዚህ ቀን በኋላ የሚከሰት ማንኛውም የደን ጭፍጨፋ ወይም የለውጥ ሂደት፣ የተሰጠውን አካባቢ ወይም የእርሻ ክፍል ከሬንፎረስት አሊያንስ ስታንዳርድ ጋር የማይጣጣም ያደርገዋል እና ይህም ለሰርቲፊኬሽን ብቁ አለመሆንን ወይም መሰረዝን ሊያስከትል ይችላል።
ሆኖም፣ ከዚህ በታች በክፍል 1.4 ላይ በዝርዝር እንደተቀመጠው፣ ሊስተካከሉ ለሚችሉ አነስተኛ የደን ጭፍጨፋ ወይም የለውጥ ሂደት አነስተኛ ጉዳዮች አንዳንድ ቅናሾች ተደርገዋል። በተጨማሪም፣ ለመሠረተ ልማት አመራር የሚከናወኑ አነስተኛ የለውጥ ሂደቶች፣ በክፍል 1.5 ላይ የተገለጸውን የጥያቄ አቀራረብ ተከትሎ በሬንፎረስት አሊያንስ ሊፈቀዱ ይችላሉ።
1.3 ከመስፈርት 6.1.1 ጋር የተገናኘ የለውጥ ሂደትን መለየት
የሬንፎረስት አሊያንስ የደን ጭፍጨፋ ስጋት ግምገማ፣ ከ2006 ዓ.ም. ጀምሮ በአንድ የእርሻ ክፍል ውስጥ የደን ጭፍጨፋ ስጋት መኖሩን ለመወሰን ከሰርቲፊኬት ባለቤቶች የተላከውን የጂኦውሂብ ይገመግማል። ከደን ጭፍጨፋ አካባቢ ጋር በሚደራረበው የእርሻ ክፍል ስፋት መቶኛ ላይ በመመስረት ሦስት የስጋት ደረጃዎች ተሰጥተዋል፦ ዝቅተኛ ስጋት (አረንጓዴ) 0%፣ መካከለኛ ስጋት (ብርቱካናማ) እስከ 1.2%፣ እና ከፍተኛ ስጋት (ቀይ) ከ1.2% በላይ መደራረብ። ዝቅተኛ ስጋት እንደ ጉልህ ያልሆነ ስጋት የሚቆጠር ሲሆን፣ መካከለኛ እና ከፍተኛ ስጋት ደግሞ እንደ ጉልህ የሆኑ ስጋት ይቆጠራሉ።
የደን ጭፍጨፋ የስጋት ግምገማ ሁልጊዜ በለውጥ ሂደት እና በሬንፎረስት አሊያንስ ትርጓሜ መሠረት ተቀባይነት ባላቸው የመሬት አጠቃቀም ለውጦች መካከል ያለውን ልዩነት ላይለይ ይችላል፤ ለምሳሌ፦
ምርታቸው ተሰብስቦ ወደ ግብርና አገልግሎት የተለወጡ፣ ነገር ግን የተፈጥሮ ስነ-ምህዳር ለውጥን የማያካትቱ የደን ልማቶች/ተከላዎች።
የጥላ ዛፎችን መሰብሰብ የተፈጥሮ ደን ለውጥን የማያካትት ሲሆን።
ከ2006 ዓ.ም. የመጨረሻ የጊዜ ገደብ በፊት የተከሰተ የዛፍ ሽፋን መጥፋት ሲኖር።
የሰርቲፊኬት ባለቤቶች አለመጣጣም ሊከሰትባቸው የሚችሉ አካባቢዎችን እና የቡድን አባላትን ለመለየት፣ ስጋቶቹን ለመገምገም እና ተገቢውን የአመራር እርምጃ ለመውሰድ የሬንፎረስት አሊያንስ የስጋት ግምገማ ውጤቶችን መጠቀም አለባቸው።
ከፍተኛ የደን ጭፍጨፋ ስጋት ያለባቸው (እንደ መካከለኛ ወይም ከፍተኛ ስጋት የተመደቡ) የእርሻ ክፍሎች ካሉ፣ የሰርቲፊኬት ባለቤቱ በእነዚህ አካባቢዎች ላይ የውስጥ ኢንስፔክሽን የማካሄድ ግዴታ አለበት። እነዚህ ኢንስፔክሽኖች ከገበሬዎች ጋር በሚደረጉ ቃለ-መጠይቆች እና በመስክ ምልከታዎች አማካኝነት ማስረጃዎችን በመሰብሰብ ማንኛውም የመሬት ለውጥ ሂደት መከሰት አለመከሰቱን ማረጋገጥ አለባቸው። የተሰበሰቡት ማስረጃዎች በኦዲት ሂደት ወቅት እና ከኦዲት በኋላ መያዝ ያለባቸው ሲሆን፣ በኦዲተሮች ወይም በሬንፎረስት አሊያንስ ሲጠየቁ መቅረብ አለባቸው። ለውጥ መከሰት አለመከሰቱን ለማረጋገጥ የሚረዱ ማስረጃዎች የሚከተሉትን ሊያካትቱ ይችላሉ፦
አስፈላጊ ከሆነ፣ የተሻሻሉ የእርሻ ድንበር ፖሊጎኖች።
በሀገሪቱ ሕግ መሠረት የመሬት አጠቃቀም መብትን ወይም ሕጋዊ የመሬት ባለቤትነትን የሚያሳዩ ሰነዶች (ለምሳሌ፡ የመሬት ባለቤትነት ማረጋገጫ፣ የሀገር በቀል መብቶች፣ የመንግስት ፈቃዶች፣ ሰርቲፊኬቶች፣ ወይም ሊረጋገጡ የሚችሉ ባሕላዊ መንገዶች)።
የጂኦ-ታግ ምልክት ያለባቸው ፎቶግራፎች፣ ካርታዎች ወይም ሌሎች የሚታዩ ማስረጃዎች።
የገበሬ፣ የማህበረሰብ አባላት እና የሌሎች ባለድርሻ አካላት የቃለ-መጠይቅ መዝገቦች።
ከአካባቢ መስተዳድር ተቋማት (ለምሳሌ፡ የደን ኤጀንሲዎች፣ ብሔራዊ ፓርኮች ወዘተ) የሚገኙ መረጃዎች።
1.4 ከመስፈርት 6.1.1 ጋር የተገናኘ ቀደም ብሎ የተከሰተ አነስተኛ የለውጥ ሂደት
ከመጀመሪያው የሰርቲፊኬሽን ኦዲት በፊት በሚደረግ የውስጥ ኢንስፔክሽን ወቅት ለውጥ ከተገኘ፣ የሰርቲፊኬት ባለቤቱ ለውጡ እዚህ በተገለጸው አነስተኛ የለውጥ ገደብ ውስጥ መሆኑን ማረጋገጥ እና በክፍል 1.4.1 መሠረት የመልሶ ማልማት/ማደስ ዕቅድ ተግባራዊ ማድረግ አለበት። ለውጡ(ጦቹ) ከተቀመጠው ገደብ በላይ ሲሆን(ኑ)፣ የሰርቲፊኬት ባለቤቱ መስፈርቱን ያላሟላውን የቡድን አባል፣ እርሻ ወይም የእርሻ ክፍል ከሰርቲፊኬሽን ፕሮግራሙ ማግለል ይኖርበታል። ለEUDR መርጦ መግባትን (opt-in) ጨምሮ ለሁሉም እርሻዎች፣ ለውጡ በታኅሣሥ 23፣ 2006 ዓ.ም. እና በታኅሣሥ 22፣ 2013 ዓ.ም. መካከል የተከሰተ መሆን አለበት። የሰርቲፊኬት ባለቤቶች እና/ወይም የቡድን አባላት እነዚህን ተጨማሪ መስፈርቶች ማሟላት አለባቸው፦
ትላልቅ እርሻዎች እና የግል እርሻዎች
በትላልቅ እርሻዎች (በቡድን ሰርቲፊኬሽን ውስጥ የተካተቱትን ጨምሮ) እና በግል እርሻዎች ላይ፣ ለውጡ ከእርሻው መሬት 1% ወይም ከ10 ሄክታር (ከሁለቱ የሚያንሰው ይወሰዳል) መብለጥ የለበትም።
የቡድን ሰርቲፊኬሽን
በቡድን ሰርቲፊኬሽን ውስጥ ለሚገኙ አነስተኛ እርሻዎች፣ ለውጡ ከጠቅላላው የእርሻ ክፍል ስፋት 1% መብለጥ የለበትም።
ሬንፎረስት አሊያንስ እነዚህን ፈቃዶች ለተወሰኑ የሰርቲፊኬት ባለቤቶች እና እንደየሁኔታው የመገምገም፣ የማጽደቅ፣ የመከልከል ወይም የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
1.4 ቀደም ብሎ ለተከሰተ አነስተኛ ለውጥ ሂደት የሚደረግ እድሳት
በእነዚህ ገደቦች ውስጥ ለሚገኙ የለውጥ ሂደቶች፣ የእርሻ አመራሩ የተለወጠውን ደን ወይም ስነ-ምህዳር ለማስተካከል ከሥነ-ምህዳር ባለሙያ ጋር በመሆን የእድሳት/መልሶ ማልማት ዕቅድ ማዘጋጀት አለበት። የታቀደው እድሳት/መልሶ ማልማት የሚከተሉትን መስፈርቶች ማሟላት ይኖርበታል፦
መጠኑ ተመጣጣኝ መሆን፦ የሚታደሰው አካባቢ ስፋት ቢያንስ ከተለወጠው አካባቢ ጋር እኩል መሆን አለበት። ይህ መስፈርት የተለወጠውን አካባቢ ከምርት ውጪ በማድረግ እና መልሶ በማደስ፣ ወይም በቅርብ በሚገኝ ሌላ አካባቢ ላይ የመልሶ ማልማት እና/ወይም የማካካሻ ጥበቃ ጥቅማጥቅሞችን በመስጠት ሊሟላ ይችላል።
እሴቱ ተመጣጣኝ መሆን፦ የሚታደሰው ስነ-ምህዳር ከጠፋው የተፈጥሮ ስነ-ምህዳር ጋር በሥነ-ምህዳራዊ እሴቱ እኩል መሆን አለበት። የሚታደሰው/መልሶ የሚለማው አካባቢ እሴት ከተለወጠው አካባቢ እሴት የሚያንስ ከሆነ ወይም ወደፊት ሊያንስ የሚችል ከሆነ፣ ሰፋ ያለ አካባቢ መልሶ መልማት ይኖርበታል።
ተጨማሪ መሆን፦ የእድሳት/የመልሶ ማልማት ተግባራቱ የተፈጥሮ እፅዋትን በተመለከተ የሬንፎረስት አሊያንስ መስፈርቶችን ከማሟላት እና ለሌሎች ምክንያቶች ከታቀዱ ተግባራት በተጨማሪ የሚከናወኑ መሆን አለባቸው።
ዘላቂ መሆን፦ የእድሳት/መልሶ ማልማት ተግባራቱ የገንዘብ ድጋፍን፣ የአመራር ኃላፊነቶችን፣ እንዲሁም ግልጽ የመሬት ድልድልን እና የመሬት መብቶችን ጨምሮ የረጅም ጊዜ ህልውናን በሚያረጋግጥ መልኩ መቀረጽ አለባቸው።
በተጨማሪም፣ በቡድን ሰርቲፊኬሽን ወቅት የሚኖር ተጨማሪ ለውጥን ለማስቀረት የሚከተሉት ተግባራዊ መሆን አለባቸው፦
ተጨማሪ የደን ጭፍጨፋን ለመከላከል ለቡድን አባላት የሚሆን የቅጣት ሥርዓት መዘርጋት።
ለቡድን አባላት የግንዛቤ ማስጨበጫ እርምጃዎችን ወይም ስልጠናዎችን መተግበር።
በስጋት ግምገማ ወቅት ከፍተኛ የደን ጭፍጨፋ ስጋት ያለባቸው ሆኖ ለተገኙ ሁሉም የቡድን አባላት የእርሻ ክፍሎች ፖሊጎን መሰብሰብ።
አመራሩ የመልሶ ማልማት ዕቅድ በfarmcert@ra.org በኩል ለሬንፎረስት አሊያንስ ማቅረብ አለበት። ዕቅዱ የሚከተሉትን ማካተት ይኖርበታል፦
ግልጽ የጊዜ ገደብ ያላቸው ግቦች እና ኃላፊነቶች ተለይተው የተቀመጡባቸው ተግባራዊ የሚደረጉ ተግባራት።
ቢያንስ በየሦስት ዓመቱ አንድ ጊዜ ተግባራዊ የሚደረግ የመልሶ ማልማት አካባቢ የክትትል ዕቅድ።
መልሶ የሚለማው አካባቢ(ዎች) ፖሊጎኖች።
የሚተከሉ የዛፍ ዝርያዎች ዝርዝር።
በየሦስት ዓመቱ የእድገት ሪፖርቶችን ለውስጥ ኢንስፔክተሮች እና ለኦዲተሮች ማቅረብ፤ ይህም ከመልሶ የሚለማው/የሚታደሰው ቦታ ወቅታዊ ሁኔታ ጋር የተጣጣሙ መሆኑን ለመገምገም እና ለማረጋገጥ ነው።
ማሳሰቢያ፦ በቡድን ውስጥ የሚገኙ አነስተኛ አምራቾች የመልሶ ማልማት ሂደቶች አፈጻጸም፣ ክትትል እና ሪፖርት አቀራረብ በቡድን አመራሩ መመቻቸት አለበት። እነዚህ እርምጃዎች ለማንኛውም የተጎዱ የቡድን አባላት ካልተከናወኑ የቡድን አመራሩ ተጠያቂ የሚሆን ሲሆን፣ ይህም ሰርቲፊኬት እንዳያገኙ ወይም እንዲሰረዝ ሊያደርግ ይችላል።
1.5 ለመሠረተ ልማት የታቀደ አነስተኛ ለውጥ ከመስፈርት 6.1.1 ጋር የተገናኘ
ለእርሻ ወይም ለምርት ማቀነባበሪያ ሥራዎች እጅግ አስፈላጊ የሆኑ መሠረተ ልማቶችን ለመጠገን ወይም ለማስፋፋት ሲባል፣ ከጠቅላላው ሰርቲፋይድ ከሆነው የመሬት ስፋት ውስጥ እስከ 1% የሚደርስ የተፈጥሮ ስነ-ምህዳር ለውጥ በሚከተሉት ሁኔታዎች ሊፈቀድ ይችላል፦
ለውጡ ሊከናወን የሚችለው አዲስ የእርሻ መሠረተ ልማት ለመዘርጋት ወይም ነባር የእርሻ መሠረተ ልማቶችን ለመጠገን ወይም ለማዘመን ብቻ ነው (ለምሳሌ፡ መንገዶች ወይም የመስኖ መሠረተ ልማቶች፣ የፓምፕ መገልገያዎችን፣ ቦዮችን፣ ኩሬዎችን፣ የውሃ ማጠራቀሚያዎችን፣ ግድቦችን እና የውሃ መያዣዎችን ጨምሮ)፣ በቋሚነት የተተከሉ ማሽነሪዎች፣ ወይም ለማጠቢያ፣ ለማቀነባበሪያ ወይም ለማሸጊያ የሚሆኑ ተቋማት።
የታቀደው የመሠረተ ልማት ዝርጋታ ወይም ጥገና የሚመለከተው ቦታ ሳይለውጥ ለምን ማከናወን እንደማይቻል የሚገልጽ ምክንያት ጨምሮ፣ የእርሻ ወይም የቡድን አመራሩ ስለ ዝርጋታው ያለውን ዕቅድ አስቀድሞ በሰነድ መያዝ አለበት።
ሊለወጥ የታቀደው የመሬት ስፋት ከተፈቀደው 1% ጠቅላላ ሰርቲፋይድ መሬት በታች መሆኑን ለማሳየት፣ የጠቅላላው ሰርቲፋይድ መሬት እና የሚለወጠው አካባቢ ፖሊጎኖች መሰብሰብ አለባቸው። ማሳሰቢያ፦ ይህ የ1% ገደብ የመጀመሪያው የሰርቲፊኬሽን ማመልከቻ ከቀረበበት ቀን ጀምሮ ያለውን አጠቃላይ የሚፈቀድ ቦታ ድምርን ያመለክታል።
ለውጡን ከመጀመሩ በፊት፣ የእርሻ ወይም የቡድን አመራሩ ከሬንፎረስት አሊያንስ ፈቃድ ማግኘት አለበት። ፈቃድ ለማግኘት አመራሩ ምክንያቶችን፣ ዕቅዱን እና የሚለወጠውን አካባቢ ፖሊጎኖች የያዘ ሰነድ በ farmcert@ra.org በኩል ማቅረብ ይኖርበታል።
ለውጡ ከሬንፎረስት አሊያንስ ስታንዳርድ መስፈርት 6.1.2 ጋር ሙሉ በሙሉ የተጣጣመ መሆን አለበት።
ለውጡ ከሚመለከተው ሕግ ጋር ሙሉ በሙሉ የተጣጣመ መሆን አለበት።
ለውጡ በቦታው ወይም በአካባቢው በተደረገ ማንኛውም የከፍተኛ የጥበቃ እሴት (HCV) ግምገማ ውስጥ ከተቀመጡ መደበኛ ምደባዎች ወይም ምክረ-ሃሳቦች ጋር የሚስማማ መሆን አለበት።
የለውጡን ዕቅድ ከገመገመ በኋላ፣ ሬንፎረስት አሊያንስ እንደ አስፈላጊነቱ የሰርቲፊኬት ባለቤቱ በክፍል 1.4.1 ላይ የተገለጸውን የመልሶ ማልማት ዕቅድ ተግባራዊ እንዲያደርግ የመጠየቅ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ይህ ፈቃድ ከአውሮፓ ህብረት የደን ጭፍጨፋ ደንብ ጋር ለተቀናጁ የኮኮዋ እና የቡና የሰርቲፊኬት ባለቤቶች አይሰራም።
1.6 ከመስፈርት 6.1.2 ጋር የተገናኘ በጥበቃ የሚደረግላቸው አካባቢዎች ላይ ያለመስፋፋት
የስታንዳርዱን መስፈርት 6.1.2 አለማክበር የሚያመጣውን ስጋት ለመገምገም፣ የሬንፎረስት አሊያንስ ስጋት ግምገማ አንድ የእርሻ ክፍል ጥበቃ በሚደረግላቸው አካባቢዎች ወይም ተለይተው በተከለሉ የጥበቃ ዞኖች ውስጥ የመገኘት እድሉን እና በእነዚህ አካባቢዎች ውስጥ የግብርና ምርት በሥራ ላይ ባለው ሕግ መሠረት የተፈቀደ መሆኑን ይወስናል።
ሬንፎረስት አሊያንስ የIUCN ጥበቃ የሚደረግላቸው አካባቢዎች ምደባን በመጠቀም "የተፈቀዱ" እና "የተከለከሉ" ቦታዎችን ለይቷል። “የተከለከሉ" ጥበቃ የሚደረግላቸው አካባቢዎች ውስጥ የግብርና ምርት የተከለከለ ሲሆን፣ "የተፈቀዱ" ጥበቃ የሚደረግላቸው አካባቢዎች ውስጥ ግን የግብርና ተግባራት በተወሰኑ ሁኔታዎች እና በሕግ በተደነገገው መሠረት ይፈቀዳሉ። በዚህ መሠረት ሦስት የሥጋት ደረጃዎች ተመድበዋል፦ አነስተኛ ስጋት (አረንጓዴ) ከጥበቃ የሚደረግላቸው አካባቢዎች ጋር ምንም ዓይነት መደራረብ የሌለበት፣ መካከለኛ ስጋት (ብርቱካናማ) "ከተፈቀዱ" ጥበቃ የሚደረግላቸው አካባቢዎች ጋር መደራረብ ሲኖር፣ እና ከፍተኛ ስጋት (ቀይ) "ከተከለከሉ" ጥበቃ የሚደረግላቸው አካባቢዎች ጋር መደራረብ ሲኖር ናቸው።
በበስጋት ግምገማ ወቅት የእርሻ ክፍሎች ከፍተኛ ስጋት ያለባቸው ሆነው ከተገኙ፣ የሰርቲፊኬት ባለቤቶች በውስጥ ኢንስፔክሽን ወቅት ሁሉንም እንደዚህ ያሉ እርሻዎችን መጎብኘት እና "በተከለከሉ" ጥበቃ የሚደረግላቸው አካባቢዎች ውስጥ የምርት ተግባር አለመከናወኑን የሚያሳዩ ማስረጃዎችን መሰብሰብ አለባቸው። ማስረጃዎቹ በኦዲት ወቅት እና ከኦዲት በኋላ መያዝ ያለባቸው ሲሆን፣ በኦዲተሮች ወይም በሬንፎረስት አሊያንስ ሲጠየቁ መቅረብ ይኖርባቸዋል። በጥበቃ የሚደረግላቸው አካባቢዎች ወይም በተጀለሉ ዞኖች ውስጥ መስፋፋት መከሰት አለመከሰቱን ለማረጋገጥ የሚያገለግሉ ማስረጃዎች የሚከተሉትን ሊያካትቱ ይችላሉ፦
አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ፣ የታረሙ የእርሻ ድንበር ፖሊጎኖች።
ከሀገር አቀፍ ሕግ ጋር የተጣጣመ የመሬት አጠቃቀምን እና/ወይም ሕጋዊ መብቶችን የሚያሳዩ ሰነዶች።
የጂኦታግ ምልክት ያለባቸው (Geotagged) ፎቶግራፎች፣ ካርታዎች እና ሌሎች ምስላዊ ማስረጃዎች።
የገበሬ እና የሌሎች ባለድርሻ አካላት የቃለ-መጠይቅ መዝገቦች።
መካከለኛ ስጋት ያለባቸው ተብለው የተለዩ የእርሻ ክፍሎች፣ የምርት ወይም የማቀነባበሪያ ተግባራት በጥበቃ የሚደረግላቸው አካባቢዎች ውስጥ መከናወን አለመከናወናቸውን እና ከሚመለከተው ሕግ ጋር የተጣጣሙ መሆኑን ለመገምገም በሰርቲፊኬት ባለቤቶች መጎብኘት አለባቸው። እንዲህ ያሉ አምራቾች ቢያንስ የሚከተሉትን ማቅረብ ይኖርባቸዋል፦
ከሀገር አቀፍ ሕግ ጋር የተጣጣመ የመሬት አጠቃቀምን እና/ወይም ሕጋዊ መብቶችን የሚያሳዩ ሰነዶች።
ከዘላቂነት ያለው ግብርና ስታንዳርድ የተወሰዱ መስፈርቶች
ይህ ክፍል ለሬንፎረስት አሊያንስ ዘላቂነት ያለው ግብርና ስታንዳርድ (SAS) ብቻ ተፈጻሚ ለሆኑ ልዩ እና/ወይም ቀጣይነት ያለው ማሻሻያ መስፈርቶች ትግበራ ተጨማሪ ዝርዝሮችን ይሰጣል።
2. ከእርሻ ድንበሮች ውጭ ያሉ የጥበቃ እና የመልሶ ማልማት አካባቢዎች
ይህ ክፍል ከዘላቂ ግብርና ስታንዳርድ ቀጣይነት ያለው ማሻሻያ መስፈርቶች 6.2.3 እና 6.2.4 ጋር በተያያዘ፣ ከሰርቲፋይድ እርሻው ውጭ የጥበቃ እና/ወይም የእድሳት አካባቢዎችን ለመጠበቅ የሚያስፈልጉ ሁኔታዎችን ያቀርባል።
2.1 ከሰርቲፋይድ እርሻው ውጭ ላሉ የጥበቃ እና የመልሶ ማልማት አካባቢዎች የተቀመጡ ሁኔታዎች ከመስፈርቶች 6.2.3 እና 6.2.4 ጋር የተገናኘ
በእርሻው ላይ የሚፈለገውን የተፈጥሮ ዕፅዋት ሽፋን መቶኛ፣ የምርት ተግባር የሚከናወንበትን የእርሻ ቦታ ሳይቀንሱ ማሳካት በማይቻልበት ጊዜ። አምራቾች በእርሻው ውስጥ ያለውን የዕፅዋት ሽፋን በሚከተሉት ሁኔታዎች መሠረት ከእርሻ ድንበሮች ውጭ በሚገኙ የጥበቃ ወይም የእድሳት/መልሰው የሚለሙ አካባቢዎች ላይ የማሟላት አማራጭ አላቸው፦
አምራቾች ከእርሻ ድንበሮች ውጭ የጥበቃ ወይም የመልሶ ማልማት አካባቢዎች ሊኖሯቸው የሚችሉት፣ በእርሻቸው ላይ የሚፈለገውን የተፈጥሮ ዕፅዋት ሽፋን መቶኛ ማሳካት ካልቻሉ ብቻ ነው።
አምራቾች በእርሻው ላይ ያለውን ነባር የተፈጥሮ ዕፅዋት ወደ ሌላ የመሬት አጠቃቀም አይለውጡም። ከእርሻ ድንበሮች ውጭ ያሉ የጥበቃ አካባቢዎች ጥቅም ላይ ሊውሉ የሚችሉት በእርሻው ላይ ያለውን ነባር እና ተጨማሪ ዕፅዋት ለማሟላት ብቻ ነው። የውጭ ጥበቃ አካባቢዎች በእርሻው ውስጥ ያለን ዕፅዋት ለመተካት ጥቅም ላይ ሊውሉ አይችሉም።
ምራቾች የሚፈለገውን የተፈጥሮ ዕፅዋት ሽፋን መቶኛ ከፊሉን በእርሻቸው ላይ፣ ከፊሉን ደግሞ ከእርሻ ድንበሮች ውጭ ባለ የጥበቃ አካባቢ ሊይዙ ይችላሉ። ለምሳሌ፦ አንድ አምራች 5% የተፈጥሮ ዕፅዋት በእርሻው ላይ እና 5% ከእርሻው ውጭ ሊኖረው ይችላል።
ከሰርቲፋይድ እርሻ ድንበሮች ውጭ ያለው የጥበቃ ወይም የእድሳት አካባቢ ቢያንስ ለ25 ዓመታት ውጤታማ የሆነ የረጅም ጊዜ ጥበቃ ሊደረግለት ይገባል።
ከሰርቲፋይድ እርሻ ድንበሮች ውጭ ያለው የጥበቃ ወይም የእድሳት አካባቢ ካለው ነባራዊ ሁኔታ አንጻር ተጨማሪ የጥበቃ እሴት እና የጥበቃ ደረጃ የሚያስገኝ መሆን አለበት፦ አካባቢው በብዝኃ ሕይወት እሴት ረገድ ተጠብቆ የሚቆይ ወይም የሚሻሻል መሆን ይኖርበታል።
ከሰርቲፋይድ እርሻ ድንበሮች ውጭ ያለው የጥበቃ ወይም የእድሳት አካባቢ ከሰርቲፋይድ እርሻው ጋር ተመሳሳይ በሆነ ስነ-ምህዳር ውስጥ የሚገኝ መሆን አለበት። ለምሳሌ፦ ሰርቲፋይድ እርሻው የሚገኝበት አካባቢ አብዛኛው ስነ-ምህዳሩ ዝናባማ ደን ከሆነ፣ የጥበቃ አካባቢውም አብዛኛው ስነ-ምህዳሩ ዝናባማ ደን በሆነበት ስፍራ መሆን አለበት።
የሰርቲፊኬት ባለቤቶች ሁሉንም መስፈርቶች የሚያሟላ የጥበቃ ወይም የእድሳት ዕቅድ ለሬንፎረስት አሊያንስ በ farmcert@ra.org በኩል መላክ አለባቸው።
2.2 ከሰርቲፋይድ እርሻው ውጭ ላሉ የጥበቃ እና የዕድሳት/መልሰው የሚለሙ አካባቢዎች ለኦዲት ዝግጁነት የተቀመጡ ሁኔታዎች ከመስፈርቶች 6.2.3 እና 6.2.4 ጋር የተገናኘ
ከእርሻ ድንበሮች ውጭ ያሉ የጥበቃ ወይም የእድሳት/መልሶ ማልማት አካባቢዎች በኦዲት ወቅት ተቀባይነት እንዲኖራቸው የሚከተሉትን መስፈርቶች ማሟላት አለባቸው፦
የሰርቲፊኬት ባለቤቶች የጥበቃ ወይም የእድሳት/መልሱ የሚለማ አካባቢውን ስፋት (በሄክታር)፣ እንዲሁም ይህ ስፋት ከሰርቲፋይድ እርሻው ስፋት አንጻር ያለውን መቶኛ መግለጽ አለባቸው።
የሰርቲፊኬት ባለቤቶች የጥበቃ ወይም የእድሳት/መልሰው የሚለሙ አካባቢዎቹ ቢያንስ ለ25 ዓመታት ውጤታማ የሆነ የረጅም ጊዜ ጥበቃ ሊደረግላቸው እንደሚችል የሚያሳዩ ሰነዶችን ማቅረብ አለባቸው።
ኦዲተሩ ቢያንስ በየሦስት ዓመቱ አንድ ጊዜ ከእርሻ ድንበሮች ውጭ ያሉትን የጥበቃ ወይም የእድሳት/መልሰው የሚለሙ አካባቢዎችን መጎብኘት አለበት። የሰርቲፊኬት ባለቤቶች ከሰርቲፋይድ እርሻ ድንበሮች ውጭ ያሉ የጥበቃ ወይም የእድሳት/መልሰው የሚለሙ አካባቢዎችን ኦዲት ለማድረግ የሚወጡ ማናቸውንም ተጨማሪ ወጪዎች መክፈል አለባቸው፤ ለምሳሌ ኦዲተሮች ማረጋገጫ ለመስጠት ወደ ጥበቃ ወይም የእድሳት/መልሰው የሚለሙ አካባቢዎች ለሚያደርጉት ጉዞ የሚወጣውን ወጪ።
በተሃድሶ ግብርና መመሪያ ውስጥ የተቀመጡ መስፈርቶች
ይህ ክፍል ለሬንፎረስት አሊያንስ ተሃድሶ ግብርና ስታንዳርድ (RAS) ብቻ ተፈጻሚ የሚሆኑ ለብቻ የተለዩ እና/ወይም ቀጣይነት ያለው ማሻሻያ መስፈርቶችን ተግባራዊ ለማድረግ የሚያግዙ ተጨማሪ ዝርዝር መረጃዎችን ይሰጣል።
3. የተፈጥሮ ሥነ-ምህዳሮች እና የእጽዋት ጥበቃ እና ልማት
ይህ ክፍል ከተለየ መስፈርት 6.2.5 ጋር መጣጣምን በተመለከተ ጠቃሚ መረጃዎችን ያቀርባል።
3.1 ከመስፈርት 6.2.5 ጋር የተገናኘ የተፈጥሮ ዛፎች ዕፅዋት ሽፋንን መጠበቅ
የሚከተሉት ተጨማሪ መስፈርቶች መሟላት አለባቸው።
አምራቾች ቢያንስ ሦስት የአገር በቀል የዛፍ ዝርያዎችን ይጠብቃሉ፣ እንዲሁም አምራቾች ስለ ዛፍ ዝርያዎች እና ጥግግት ብሔራዊ የጥቆማ ሃሳቦችን ይከተላሉ።. | |
ሌሎች መረጃዎች
ይህ ሰነድ ለመጀመሪያ ጊዜ የታተመበት ቀን (ቁ. 1.0)፦ ሐምሌ 1፣ 2014 ዓ.ም.
ሰርቲፊኬሽን ለማግኘት “አስገዳጅ” ተብለው የተጠቀሱ ሰነዶች መሟላት አለባቸው። “አስገዳጅ ያልሆኑ” ተብለው የተጠቀሱ ሰነዶች፣ አንባቢዎች መስፈርቶችንና ሌሎች አስገዳጅ ይዘቶችን እንዲረዱና እንዲተገብሩ ለመርዳት አስገዳጅ ያልሆኑ መረጃዎችን ይሰጣሉ።
የትርጉም ማሳሰቢያ
በትርጉም ውስጥ ባለው መረጃ ትክክለኛ ትርጉም ላይ ለሚነሱ ማናቸውም ጥያቄዎች፣ ግልጽነት ለማግኘት ይፋዊ የእንግሊዝኛ ቅጂን ይመልከቱ። በትርጉም ምክንያት የሚፈጠሩ ማንኛውም ስህተቶች ወይም የትርጉም ልዩነቶች አስገዳጅ አይደሉም እና ለኦዲት ወይም ለሰርቲፊኬሽን ዓላማዎች ምንም ውጤት አይኖራቸውም።
ይህንን ይዘት ከሬንፎረስት አሊያንስ ቅድሚያ የጽሑፍ ፈቃድ ውጭ ማባዛት፣ ማሻሻል፣ ማሰራጨት ወይም እንደገና ማተም በጥብቅ የተከለከለ ነው።
ተጨማሪ መረጃ?
የሬንፎረስት አሊያንስ ሰርቲፊኬት ለማግኘት እርዳታ ለማግኘት የደንበኛ ስኬት ቡድናችንን customersuccess@ra.org ላይ ያግኙ።
ስለ ሬንፎረስት አሊያንስ የበለጠ መረጃ ለማግኘት፣ http://www.rainforest-alliance.org ይጎብኙ፣ info@ra.org ላይ ወይም የሬንፎረስት አሊያንስ አምስተርዳም ቢሮ፣ De Ruijterkade 6፣ 1013AA Amsterdam፣ The Netherlands ያግኙን።